የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) የእንግሊዝ መንግሥት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን ያደረገው የቴክኖሎጂ ድጋፍ የጋራ ደኅንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል።
የእንግሊዝ መንግሥት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን ያደረገው 25 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የቴክኖሎጂ እገዛ የርክክብ መርሐ ግብርና ጉብኝት በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የአቪዬሽን ደኅንነት ዋና መምሪያ ተከናውኗል።
የኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዳረን ዌልች የተመራ ልዑካን እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት መርሐ ግብሩ ተካሂዷል።
የአቪዬሽን ደኅንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አስራት ቀጄላ ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ደኅንነት ዘርፍ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን በብቃት በማሟላት ተጠቃሽ ሀገር መሆኗን አረጋግጠዋል።