በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብረሃም ንጉሴ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች የመስክ ጉብኝት እያደረጉ ነው። አምባሳደር አብረሃም ንጉሴ የግብርና ቴክኖሎጂ፣ ጤና፣ ፈጠራ እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ያተኮሩ ስራዎች እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በሳይበር ደህንነት፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በዘመናዊ የህክምና መሠረተ ልማት ላይ ያለው ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚደርስ ጠቁመዋል።
የእስራኤል የቴክኖሎጂ ተቋማት የኢትዮጵያን ዲጂታላይዜሽን ለመደገፍ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል። የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እና ታሪካዊ ቅርሶች ለኢኮኖሚና ዲፕሎማሲዊ ትስስር ዋና ምሰሶዎች መሆናቸውን አመልክተዋል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዮሐንስ ፋንታ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የተለያዩ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እንዲያመጡ ጥሪ አቅርበዋል። መንግሥት ለባለሀብቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ማበረታቻ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።