ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጋሞ ዞን የሚገኘውን ዮ ሆልዲንግ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ጎብኝተዋል። የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ እንደሚቻል ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የተፈጥሮ ሀብትን በጠንካራ ስራ በሀገር ውስጥ ማልማት የኢኮኖሚ ልዕልናን የሚያረጋግጥ ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ፋብሪካው በነሐሴ 2017 ዓ.ም ሥራ ጀምሯል። የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት በአገር ውስጥ በመተካት ከውጭ የሚገባ ምርትን እንደሚቀንስ እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።