ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በወልድያ ከተማ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችን በመርቀት ሺህ ጠላት ቢሰበሰብ የኢትዮጵያን ጉዞ ለአፍታም እንደማያስቆመው ተናግረዋል።
በወልድያ ከተማ በአመራሩና በሕዝቡ ትብብር የተገነቡ ፕሮጀክቶች በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተገኝተው ተመርቀዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ወልድያ የልማት፣ የፅናትና የድል አምባ ናት ሲሉ የከተማዋን ማዘመንና የንግድና ኢንዱስትሪ ማዕከላትን ማስፋፋት ወደፊት የመገስገስ ማረጋገጫ እንደሆኑ ገልጸዋል።
የእኛ መንገድ መደመር፣ ግባችን ደግሞ ብልጽግና ነው ሲሉም ትግላችን ከመንገድ ክፍፍልና ድህነትን ከፈለጉ ጋር እንደሆነና የኢትዮጵያን ልዕልና ሳናረጋግጥ እንደማንቆም አጽንኦት ሰጥተዋል።