የመደመር መንግሥት በግብርናና መሰረተ ልማት ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን አስታውቋል።
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 126 ነጥብ 69 ሚሊየን ኩንታል የመስኖ ስንዴ ምርት ተገኝቷል።
በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊየን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ኩንታል ምርት መሰብሰብ ተችሏል። የግብርና ዘርፉ 7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለቀጣዩ ትውልድ ፍላጎት የተስማሙ ከተሞችንና መንደሮችን ለመገንባት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርና ሌሎች ፕሮጀክቶች በመተግበር ላይ ናቸው።