ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር “ተስፋን መትከል” በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአረንጓዴ ዐሻራ ውጤት አረንጓዴ ወርቅ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም አፈርን ከመሸርሸር መጠበቅ፣ የተረበሸን ማንነት ማከም እና ብሔራዊ ስነልቦናን መገንባት እንደሆነ አስረድተዋል።
በዚህ ዓመት 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን ጠቁመው 65 ቢሊየን ችግኞች የመድረስ ትልማቸውን አስታውሰዋል። ዜጎች ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለትውልድ አረንጓዴ ውርስ እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ይህ ሥራ ከተፈጥሮ የመታረቅና በልማት የመላቅ አዲስ ጎዳና ነው።