ኢትዮጵያ የዓለም የአካባቢ ጥበቃ ቀንን አስመልክቶ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን እንደተከለች አስታወቀች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው መርሃ ግብር የደን ሽፋንን ከ11.2 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ አድርጓል።
በዚህ አመት 9.2 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። ከእነዚህ ውስጥ 40 በመቶው ለደን ልማት ሲሆን ቀሪው ለምግብና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ይውላል።
መርሃ ግብሩ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ስራ አስገኝቷል። ኢትዮጵያ በ2030 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ቁጥር 400 ሺህ ለማድረስ አቅዳለች።