የአፋር ክልል የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በዛሬው እለት ተጀመረ።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ተገኝተዋል። እሳቸውም ክልሉ ማንኛውንም ዓይነት እጽዋት ማፍራት የሚችል ከፍተኛ አቅም እንዳለው ተናግረዋል።
መርሃ ግብሩ የክልሉን የተፈጥሮ ሚዛን ከመጠበቅ ባለፈ ለቀጣይ ትውልድ ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና መሰረት እንደሚጥል አብራርተዋል። በክልሉ የሚከናወኑ ዘላቂ የልማት ስራዎች በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ አርአያ ሊሆኑ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ እንደገለጸው በአረንጓዴ ዐሻራ ዘርፍ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ርዕሰ መስተዳድሩ ማህበረሰቡ በችግኝ ተከላ ስራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።