የጋምቤላ ክልል የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጋምቤላ ከተማ ተጀምሯል።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ የአቅመ ደካማ ወገኖች የቤት ግንባታ ስራ ተጀምሯል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በጎነት የጤናማ ማህበረሰብ ዋነኛ መገለጫ እንደሆነ ተናግረዋል።
የክልሉ ተቋማት፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች አካላት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።