በአፋር ክልል ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የተቀናጀ የጤና ዘመቻ ተጀምሯል። መርሐ ግብሩ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ዘመቻውን በማስጀመር ላይ ተገኝተው የተቀናጀ ሥራ አስፈላጊነት አመልክተዋል። በተለይም ተማሪዎችን ጤና ማሻሻል ላይ ትኩረት እንደተደረገ ገልጸዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን ሐቢብ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሣ አደም በተለያዩ ወረዳዎች የሚካሄደው መርሐ ግብር የተማሪዎችን የወደፊት ጤና ለማረጋገጥ ያገለግላል ብለዋል።
መርሐ ግብሩ በክልሉ 11 ወረዳዎች ባሉ ትምህርት ቤቶች ይተገበራል።