የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የሕጻናትን ትምህርት በጨዋታ መሰረት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። ይህም በዓለም አቀፍ የጨዋታ ቀን ወቅት ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው መርሐ ግብር ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዳይሬክተር አቶ ሸምሰዲን ኢብራሂም ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በራይት ቱ ፕሌይ ድርጅት የቢሾፍቱ ሉሜ ፕሮጀክት ማኔጀር ሙሉጌታ ጋቢሳ ፕሮጀክቱ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን በቢሾፍቱና ሉሜ ወረዳ በመተግበር ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከ75 ሺህ በላይ መጽሐፍትም ተደራሽ መደረጉን ጠቁመዋል።