ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦሌ ክፍለከተማ የተገነቡ የስፖርትና መዝናኛ መሠረተ ልማቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ከንቲባዋ በግንቦት 16 ቀን በቦሌ ክፍለከተማ የተገነቡ አምስት ስፖርት ማዘውተሪያዎችን፣ 95 የህጻናት መጫዎቻዎችን፣ ስድስት የህጻናት ማቆያዎችን እና ሌሎች መገልገያዎችን በይፋ መርቀዋል።
ካፒቴን አበራ ለሚ በ300 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በ4900 ካሬ ሜትር ላይ የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየምን ገንብተው አስረክበዋል። ስታዲየሙ የእግር ኳስ ሜዳ፣ የመሮጫ ትራክ፣ ጂምናዚየም እና ለወጣቶች ሱቆችን ያካትታል።
ከንቲባዋ ካፒቴን አበራ ለሚን አመስግነው ነዋሪዎች መሠረተ ልማቶቹን በእንክብካቤ እንዲጠቀሙባቸው ጠይቀዋል።