የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወቅት የጽዳት ንቅናቄን አስጀምረዋል።
ከንቲባዋ የጽዳት ሥራ ከራስ፣ ከቤት እና ከአካባቢ የሚጀመር የዕለት ተዕለት ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ በየጊዜው በአረንጓዴ እየለማችና እየጸዳች እንደምትገኝ ጠቁመው ትኩረት የሚሹ አካባቢዎችና ሰፈሮች እንዳሉ ተናግረዋል።
የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓትን ለማዘመን ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል ሲሉ ደረቅ ቆሻሻ ሀብት በመሆኑ በአግባቡ በመለየት ማስወገድ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።
የክረምት ወራት የፍሳሽ መውረጃዎችና የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ለበሽታ እንዳይዳርጉ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።