የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል ዘመናዊ የፎረንሲክና የሥነ ምረዛ ምርመራ ልሕቀት ማዕከልን መርቀዋል።
ከንቲባዋ በዚህ ወቅት ማዕከሉ በሳይንሳዊ መንገድ የተሟሉና ዘመኑን የዋጁ መሳሪያዎችን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ማዕከሉ የፎረንሲክ፣ የዘረመልና የሥነ ምረዛ አገልግሎትን በአንድ መስኮት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
በሀገሪቱ አምስት ብቻ የሆኑ የፎረንሲክ ተቋማት መካከል ይህ ማዕከል 80 የአስክሬን መመርመሪያ መሳሪያዎች ያሉት ሲሆን ለፍትሕ ሥርዓቱ ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።