የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከጋምቤላ ክልል ጋር በቀዳማይ ልጅነት እንክብካቤ እና በሌሎች ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለመተባበር ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ ጋር የተደረገውን ውይይት አመልክተዋል።
በዚህ ውይይት ሁለቱም አካላት በቀዳማይ ልጅነት እንክብካቤ፣ በኮሪደር ልማት እና በሌሎች የሰው ተኮር ስራዎች ልምድ ለመለዋወጥ ተስማምተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የጋምቤላ ክልል በጋራ ለመስራት ትብብራቸውን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል።