ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ በአዲስ አበባ ተጀምሯል። የአፍሪካ ሕብረትና የኢጋድ ባለሥልጣናት ሒደቱን ደግፈዋል።
በሐምሌ 9 2018 በተጀመረው ጉባዔ ላይ የአፍሪካ ሕብረት የፖለቲካ ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ ተገኝተው ሒደቱ ለአፍሪካ ሰላም ግንባታ መልካም ተሞክሮ እንደሚሆን ተናግረዋል።
የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ ደግሞ ጉባዔው ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የተሻለ ተስፋና ዕድገት እንደሚያመጣ አረጋግጠዋል።
ከጋምቤላ ክልል የመጣች አንዲት ተሳታፊ በጉባዔው ላይ ሳለች ወንድ ልጅ ተገላግላ ስሙን “ምክክር” ብላ ሰይማለች። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለእናትና ለልጇ ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግራለች።