በአዲስ አበባ የተጀመረው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የንዑስ ቡድኖች ውይይት ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጥሏል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ታሪካዊ ጉባዔውን በአዲስ አበባ በይፋ ጀምሯል። የመጀመሪያዎቹ አራት ቀናት በቅድመ ምክክር ካሳለፈ በኋላ ሐምሌ 13 ቀን ወደ ዋናው ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በስምንት ብሔራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በ80 ንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው ይወያያሉ። እያንዳንዱ ንዑስ ቡድን 50 ተመካካሪዎችን ይይዛል። ሒደቱ ሐምሌ 15 ቀን ድረስ ይቀጥላል።
ከ80 ባለሙያዎች የተቋቋመ የባለሙያዎች ስብስብ በአጀንዳዎቹ ላይ ማብራሪያ ይሰጣል። ከ50 በላይ ገለልተኛ ታዛቢዎች ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ሰብዓዊ መብት ተቋማት ሒደቱን ይታዘባሉ። 160 አመካካሪዎችና 256 የቃለ ጉባዔ ጸሐፊዎች ተመድበዋል።