የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ የውይይት ምዕራፍ በ80 ንዑስ ቡድኖች በይፋ መጀመሩን አስታወቀ።
ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር የንዑስ ቡድን ውይይት የሀገራዊ ምክክሩ ቁልፍ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ተመካካሪዎች በተመደቡባቸው ስምንት አጀንዳዎች ላይ ሐሳባቸውን ያቀርባሉ።
እያንዳንዱ ዐቢይ የሥራ ቡድን 10 ንዑስ ቡድኖችን ያካተተ ሲሆን በአጠቃላይ 80 ንዑስ ቡድኖች ተቋቁመዋል። ተመካካሪዎቹ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ በቅድመ ምክክር ውይይቶች ተሳትፈዋል።
ኮሚሽኑ 160 አመካካሪዎችን እና 256 የቃለ ጉባኤ ጸሐፊዎችን ለመደገፍ አሰማርቷል። ይህ ሂደት በአዲስ አበባ ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎችን ያሳትፋል።