ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ በይፋ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዝግጅቱ ላይ እንደተናገሩት ቀይ ባሕርን ያጣነው በውስጥ ስንጨቃጨቅ ጊዜ የውጭ ሃይሎች ጣልቃ በመግባት ነው።
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ይህ ምክክር ቀጣናውን ወደ ብሩህ ተስፋ የሚመራ እርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል።
በአፍሪካ ህብረት የፖለቲካ ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ ምክክሩ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ እንደሚሆን አስታውቀዋል።