የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ሲሆን ከነገ ጀምሮ በቡድኖች የተዘጋጁ ሪፖርቶች ላይ ምክክር ይጀመራል። ከአራት ሺህ በላይ ተመካካሪዎች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) በዛሬው መግለጫ ምክክሩ ከሐምሌ 8 ጀምሮ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን አመልክተዋል። ተመካካሪዎች በቡድን ተከፋፍለው አጀንዳዎችን በመደማመጥና በመከባበር ወደ ሀሳብ ማጠናቀር ተሸጋግረዋል።
ከነገ ጀምሮ አስር አባላት ያሏቸው ቡድኖች ያጠናቀሯቸውን ሪፖርቶች ወደ 50 በመሰባሰብ ምክክር ይጀምራሉ። በታሪክ፣ በፌደራሊዝምና በማንነት ጉዳዮች ላይ ባለሙያዎች ገለጻ አቅርበዋል።
የአሰላ ከተማ ነዋሪዎች ምክክሩ የህዝቡን አንድነት በማጠናከር ሰላምና ልማትን ያረጋግጣል ሲሉ ተናግረዋል። ተቋማት የጤና፣ የጸጥታና የትራንስፖርት ድጋፍ አድርገዋል።