የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ዓመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጠናቋል። ተሳታፊዎች 26 ነጥብ ያለው የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ጉባኤው በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተካሂዷል። የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ተገኝተዋል።
በመግለጫው በሰላምና ጸጥታ፣ ሰብአዊ መብት እና ዘላቂ ልማት ላይ ትብብር ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። በአፍሪካ ያሉ ግጭቶችን በዲፕሎማሲ መንገድ ለመፍታት እና ለሰላም ማስከበር ስራዎች አስተማማኝ ፋይናንስ ለማረጋገጥ ተስማምተዋል።
ተሳታፊዎች ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተጽእኖ ላይ በቡድን 20 እና ቡድን 7 ስብሰባዎች የአፍሪካን ድምጽ ለማሰማት ተስማምተዋል።