የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመጽሐፉ ምረቃ ላይ ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባን እድገት የሚዘክረው አዲስ እንደ አዲስ የተሰኘው መጽሐፍ በይፋ ተመርቋል።
በመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጽሐፉ ለህዝባችን ቃል ገብተን ቃላችንን በተግባር የቀየርንበትን ታሪክ የሚተርክ ነው ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ደግሞ የተከናወነው ለውጥ በብዕር ተከትቦ ለታሪክ ማጣቀሻነት በሚበቃ መልኩ ቀርቧል ብለዋል።
እንግሊዛዊው ጸሐፊ ፕሮፌሰር ስሞን ሊ፣ ዶ/ር ክሌመንት ካቱሉሺ፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ሂርዩ ቁምቢ እና ቡድናቸው መጽሐፉን በጋራ ጽፈዋል። ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እና ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።