ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ካደረጉ በኋላ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ።
ይህ ድርጊት የምክር ቤቱ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በኋላ ተከናወነ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አከናውነናል ሲሉ ገልጸዋል።
በዚህ አጋጣሚ ተስፋን መትከላችንን እንቀጥላለን ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በዛሬው ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።