ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ዕዳ አስተዳደርን አመለከቱ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ዋና ዋና ነጥቦችን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የንግድ ብድር ለልማት እንደማያስፈልግ ገልጸዋል።
ከሁለት ዓመት በፊት የዩሮ ቦንድ ጉዳይ ተነስቶ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከብዙ አበዳሪዎች ጋር ተስማምታ ዕዳውን ከ50 በመቶ በላይ ከነበረበት ወደ 45 በመቶ በታች እንዳወረደች ተናግረዋል።
ይህ ለተቋማት እምነት እንዲገኝ አድርጓል ብለዋል። ከቡድን ሀያ ሀገራት ጋር ስምምነት ተፈርሟል። ለሀገር ውስጥ ብድር ደግሞ የመክፈል ቁመና ማረጋገጥ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።