የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ቁጠባን መሰረት ያደረገ የበጀት አጠቃቀም አስፈላጊ መሆኑን አስታውቀዋል። ይህም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተደረገ ውይይት ላይ ነው።
አዲስ አበባ ሰኔ 22 2018 በተካሄደው የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ አቶ አሕመድ ሽዴ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ 2 ትሪሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ቅድሚያ የሚሰጣቸውን በመለየት ደረጃ በደረጃ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራም አብራርተዋል።
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጀት ጋር በተያያዘ ጥናት እየተደረገ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ የዩኒቨርሲቲ ጤና ፕሮጀክቶች ወጪ ላይ የክልል መንግሥታት ኃላፊነት ሊወስዱ እንደሚችሉ አመልክተዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ የበጀት አመዳደብ ዕቅድ የሀገሪቱን 10 ዓመት መሪ ዕቅድ መሰረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የውጭ ዕዳ መጠን ወደ 1 ነጥብ 4 በመቶ መቀነሱንና 30 በመቶው በጀት ለዕዳ ክፍያ እንደሚውል አብራርተዋል።