የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በልዩ ስብሰባው ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተደረጉ ሶስት የብድር ስምምነቶችን አጸደቀ።
በአዲስ አበባ የተካሄደው ስብሰባ የ437 ሚሊየን 400 ሺህ ኤስ.ዲ.አር ብድር ለዘላቂ እድገት ፖሊሲ፣ 145 ሚሊየን 500 ሺህ ኤስ.ዲ.አር ለመሬት አያያዝ ፕሮግራም እና 54 ሚሊየን 600 ሺህ ኤስ.ዲ.አር ለመስኖ ልማት ፕሮጀክት አጽድቋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ስምምነቶቹ የልማት ተግባራትን እንደሚያጠናክሩ እና የወጣቶችን፣ ሴቶችን እና አርሶ አደሮችን ህይወት እንደሚያሻሽሉ ተናግረዋል።
እነዚህ ስምምነቶች ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት ይረዳሉ ብለዋል።