የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የክልሉ ሕዝብ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ሽመልስ ባለፉት ሰባት ዓመታት በክልሉ ከ28 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውንና 85 በመቶው መጽደቃቸውን ገልጸዋል። በዚህም የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 29 በመቶ ማደጉን አመልክተዋል።
በዘንድሮው መርሐ ግብር በአንድ ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል መታቀዱን አመልክተዋል። መርሐ ግብሩ በነገው ዕለት እንደሚጀምር ጠቁመው ሕዝቡ በነቂስ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በበኩላቸው አረንጓዴ ዐሻራን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀለም እንደሆነ ገልጸዋል።