የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግንባር ቀደም መሆኗን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማትን በማጠናከር ለነገው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው አለ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ ተፈጥሮ ለኛ ከተሰጠ ሀብትነት ባሻገር ለመጪው ትውልድ የምናስተላልፈው አደራ ጭምር ነው ብለዋል። ዋልያ አይቤክስ፣ ቀይ ቀበሮ፣ ጭላዳ እንዲሁም በርካታ አዕዋፋትና አበቦች የሀገራችን ማንነት እና የኢኮኖሚያችን አቅም ናቸው ሲሉም አውስተዋል።
ከ60 ዓመታት በፊት በሁለት ብሔራዊ ፓርኮች የተጀመረው ዘመናዊ የጥበቃ ጉዞ ዛሬ ላይ እንደ ሀገር ከ30 በላይ መድረሱን እንዲሁም በርካታ የዱር እንስሳት መጠለያዎች ከ106 በላይ ልዩ ልዩ የዱር እንስሳት ጥበቃ ቦታዎች መፈጠራቸውን ተናግረዋል።