የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመሰል በጄኔቫ በሚካሄደው 68ኛው የዓለም አእምሯዊ ንብረት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር አድርገዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ኢትዮጵያ ፈጠራንና ዘላቂ ልማትን ለማበረታታት የሕግና ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን እንዳደረገች ገልጸዋል።
አእምሯዊ ንብረት ለኢኮኖሚ ሽግግር፣ ለኢንቨስትመንትና ለኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የአእምሯዊ ንብረት ማዕቀፏን በማዘመንና በቁልፍ አለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ በመሳተፍ ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።
ዋና ዳይሬክተሩ ከብሪክስ አባል ሀገራት ባለስልጣናት ጋር በመወያየት በህንድ ለሚካሄደው ስብሰባ አጀንዳዎች ላይ ተስማምተዋል።