የሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ በቅርሶች ጥበቃና ልማት ላይ ያተኮሩ ሥራዎችን አከናውኗል።
የቅርስ ዳይሬክተር አሚር ረመዳን እንዳሉት ባለፉት ዓመታት ታሪካዊ ቅርሶችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ መንገዶች በሕዝብ ተሳትፎ ተሠርተዋል። 6 ሺህ 114 ካሬ ሜትር የሚሸፍነው የጀጎል ግንብ ዙሪያ አረንጓዴ ስፍራ ተደርጓል።
እነዚህ ሥራዎች ከ7 ሺህ በላይ ዜጎችን የሥራ እድል ፈጥረዋል። በቀጣይም የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስ ጥበቃ ሥራዎች ይቀጥላሉ።