የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም ከማስቻሉ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።
የክልሉ የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት በማጃንግ ዞን በመንገሺ ወረዳ ተካሂዷል።
ርዕሰ መስተዳድሯ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎችን በማጠናከር ለግብርና ልማቱ ስኬታማነት መተጋገዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስራዎች በርካታ ስኬቶች መገኘታቸውንና የተራቆቱ አካባቢዎች ከማገገማቸው ባለፈ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመረውን ልማት በማሳለጥ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ እንዳለበትና የክልሉ ህዝብ ተሳትፎና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።