የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ችግኝ በመትከል የዓመታዊ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሩን በይፋ አስጀምሯል። ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን መርሐ ግብሩ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ስትራቴጂክና ከፍተኛ አመራሮች በብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ችግኝ በመትከል የተቋሙን ዓመታዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ በይፋ አስጀምረዋል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ባለፉት ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን አስታውቀዋል።
መርሐ ግብሩ የተራቆተ መሬትን በተለያዩ ተክሎች በማልበስ የደን ሽፋንን ማሳደግ መቻሉንና የአካባቢ ሥነ ምኅዳር ደህንነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።