የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ በክልሉ 43 ከተሞች ውስጥ የኮሪደር ልማት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አስታውቋል። ቢሮው ኃላፊ ዶክተር ሞላ መልካሙ እንደተናገሩት ሥራው ከተሞቹን ምቹ የሥራ፣ የመኖሪያና የቱሪዝም መዳረሻዎች እያደረጋቸው ነው።
የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ሞላ መልካሙ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በሚገኙ 43 ከተሞች ውስጥ ማዘጋጃ ቤቶችን ጨምሮ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ በስፋት እየተካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል።
የወልድያ ከተማን የኮሪደር ልማት መመልከታቸውን ጠቁመው ሥራው በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ አስደናቂ ሒደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
የኮሪደር ልማት ከከተማ ውበት እና ገጽታ ባለፈ ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ ጠቀሜታን እያስገኘ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በሌሎች ከተሞች የሚከናወኑ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።