ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጋሞ ዞን የሚገኘውን የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ጎብኝተው የግል ጥቅምን በመተው ለሀገር የወል ጥቅም ቅድሚያ መስጠት እንደሚያስፈልግ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት በጋሞ ዞን የሚገኘውን ‘ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ጎብኝተዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ 5 ቢሊየን ዶላር ገደማ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉን ገልጸዋል። ካለፈው ዓመት መጨረሻ ወዲህ አራት የድንጋይ ከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ ሥራ መግባታቸውን አመልክተዋል።
በቀጣይ ተጨማሪ ፋብሪካዎች ወደ ሥራ እንደሚገቡ ጠቁመው የድንጋይ ከሰል ምርቶችን ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ሰፊ መሆኑን ተናግረዋል። የድንጋይ ከሰል ምርቶቹ የጥራት ችግር እንደሌለባቸው አመልክተዋል።