የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ባሕላዊ ዳኝነትን በማጠናከር ላይ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል። የባህል ሽማግሌዎች ፎረም በሰላም ግንባታ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው።
የቢሮው የባሕል ዘርፍ ኃላፊ ደግነህ ቦጋለ ባሕላዊ ዳኝነት አለመግባባቶችን በመፍታት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሆነ ተናግረዋል።
በቅርቡ የባህል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ጸድቆ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ይህም ወንጀሎችን በእጅጉ እንዲቀንስ እና የማሕበረሰቡ ትስስር እንዲጠናከር አድርጓል።
የባህል ሽማግሌዎች ፎረምን ለማጠናከር በሆሳዕና ከተማ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ባሕላዊ ዳኝነት በግልግል እና በዕርቅ ግጭቶችን ይፈታል።