የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተለያዩ ዙሮች በስኬት እየተካሄደ መሆኑን አስታውቋል።
ፈተናው በበይነ መረብ በስድስት ዙሮች እና በአንዳንድ አካባቢዎች በወረቀት በአራት ዙሮች እየተሰጠ ነው።
በትግራይ ክልል 14 ሺህ 755 ተፈታኞች በበይነ መረብ ፈተናቸውን ከሰኔ 23 ቀን 2018 ጀምሮ እየወሰዱ ነው።
በወረቀት ለመፈተን የተመዘገቡ 15 ሺህ 325 ተፈታኞች ፈተናቸውን ከሐምሌ 22 እስከ 24 ቀን 2018 በመቐለ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ይወስዳሉ።