የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ የባለድርሻ አካላት ተባብረው እንዲሰሩ አሳሰቡ።
በአዲስ አበባ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደ ምክክር ላይ ብርሀኑ ነጋ የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
ፈተናው ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት ይካሄዳል። ከ563 ሺህ በላይ ተፈታኞች ተመዝግበዋል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፈንታ የጸጥታ ዘርፉ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ጥብቅ ርምጃ እንደሚወሰድ አረጋግጧል።