ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 807 ተማሪዎችን እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 279 ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች አስመርቋል።
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለ20ኛ ዙር 807 ተማሪዎችን በጤና፣ በምህንድስና፣ በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ በግብርናና ተፈጥሮ ሃብት እንዲሁም በሕግ መስኮች አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው የተግባር ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ በተግባር የሰለጠኑ ተማሪዎችን እያስመረቀ መሆኑን ተናግረዋል።
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በተከታታይ የትምህርት መርሐ ግብር በመጀመሪያ ዲግሪ 279 ተማሪዎችን አስመርቋል።