በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በ640 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በዛሬው ዕለት ተመርቋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በ640 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ (ኢ/ር) እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የወራቤ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በከተማዋና አካባቢው ለዓመታት ይስተዋል የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና ጥራት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡