የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዘላቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይልን በሀገሪቱ ሁሉ ተደራሽ ለማድረግ ስትራቴጂ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል። ይህም በብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሐ ግብር ሦስተኛ ምዕራፍ ትግበራ ላይ በተደረገ አውደ ጥናት ተገልጿል።
የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ሱልጣን ወሊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በተመጣጣኝ ዋጋ ታዳሽ ኃይል ተደራሽነት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኃይል ማመንጫ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ይጠናከራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌቱ ገረመው መርሐ ግብሩ እስከ 2035 ድረስ ሀገሪቱን ሙሉ በሙሉ ለማስተካከል ያለመ መሆኑን አስታውቀዋል።
የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሐ ግብር ሦስተኛ ምዕራፍ ከ18 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልገዋል። እንዲሁም የኢነርጂ ፖሊሲ ክለሳ በመደረግ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እንዲያድግ ይደረጋል።