የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአገሪቱ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን የአፍሪካ ታዳሽ ኃይል ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው።
ተቋሙ የኃይል ማመንጫዎችን፣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስፋፊያ መስመሮችን በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጓል። ከፍተኛ ፍላጎት ባላቸው አካባቢዎች ያሉ ነባር ግንባታዎችን በማዘመን እና ተጨማሪ ማስፋፊያ ሥራዎችን በመከወን ላይ ይገኛል።
የደብረ ማርቆስ እና ባህር ዳር ኮሪደር በማስፋፊያ ሥራዎቹ ውስጥ ይገኛሉ። የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 55 በመቶ ደርሷል።
የእንጅባራ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከዓለም ባንክ በተገኘ 19.5 ሚሊየን ዶላር ብድር ይገነባል።