በ2018 በጀት ዓመት ከ18 ሚሊየን በላይ የሀገር ውስጥ ዜጎች በአማራ ክልል የቱሪስት መዳረሻዎችን ጎብኝተዋል።
የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ መልካሙ ጸጋዬ እንደተናገሩት በዓመቱ ከ58 ሺህ የውጭ ሀገር ዜጎችም መስህቦቹን ተመልክተዋል። ጎብኚዎች ከ11 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አስገኝተዋል።
ቢሮው የመስህብ ሀብቶችን ለማልማት 41 የመዳረሻ ልማት ስራዎችን አከናውኗል። ከእነዚህ መካከል 9 ሙዚየሞች ይገኙበታል። መንግስት ለዚህ ከ111 ሚሊየን ብር በላይ በጀት መድቧል።
በተጨማሪም 19 ተዘርፈው የወጡ ቅርሶችን ማስመለስ ተችሏል። በ2019 በጀት ዓመት ከ100 ሺህ የውጭ ጎብኚዎችን ለመሳብ እቅድ ተይዟል።