አዲስ አበባ በተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተለወጠች ሲሆን የአፍሪካ የፖለቲካና ዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን እያጠናከረች ነው።
ከተማዋ ጠባብ መንገዶችን ወደ ሰፊና ዘመናዊ ጎዳናዎች በመቀየር እንዲሁም ረጅም የእግረኛ መሄጃዎችን፣ አረንጓዴ ቦታዎችንና የብስክሌት መስመሮችን በመገንባት ላይ ትገኛለች። ይህ ልማት ለሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ እድል ፈጥሯል።
ከተማዋ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በመሆን የበርካታ ሀገራት ኤምባሲዎችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ማዕከል ሆናለች። ከኒውዮርክና ጄኔቫ ቀጥላ በዓለም የዲፕሎማሲ ከተማ ለመሆን በቅታለች።
እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክና ወዳጅነት አደባባይ ያሉ ቦታዎች ከተማዋን ለቱሪስቶችና ባለሀብቶች ማራኪ አድርገዋታል። ኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ130 በላይ ከተሞችን በቀጥታ በማገናኘት ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን ለማስተናገድ አስችሏታል።