የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ አገልግሎቶች ከ42 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ሰብስቧል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በበጀት ዓመቱ በአየርና በድንበር 7 ነጥብ 2 ሚሊየን መንገደኞችን አገልግሎት እንደተሰጠ ተናግረዋል።
ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ፓስፖርቶች ተሰጥተዋል። የአገልግሎት ቅርንጫፎች ወደ 23 ተደርሰዋል። ከ1 ሚሊየን በላይ የውጭ ዜጎች አገልግሎት ተቀብለዋል።
በተጨማሪ 4ሺህ 883 ዜጎች በሐሰተኛ ሰነድ ተይዘዋል። 55ሺህ በላይ ሰዎች በህገወጥ መንገድ መንቀሳቀስ ሲሞክሩ ተይዘዋል።