የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ በፌዴራልና በክልል ደረጃ በተጀመሩ 37 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ከ3 ሺህ 300 በላይ አገልግሎቶች ለዜጎች እየተሰጡ መሆኑን አስታወቁ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።
መኩሪያ ኃይሌ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የመሶብ ማዕከላትን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን እና የሙያ እና የሥራ ኢንዱስትሪ ምድብ ሰነድ ወደ ትግበራ መግባቱን ተናግረዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ ዜጎች ጊዜ፣ ጉልበትና ሀብት ሳያባክኑ አገልግሎት እንዲያገኙ የተጀመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስታውቀዋል።