በጅማ ዞን ሊሙ ገነት ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀምሯል። አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ ሲሆን ለሕብረተሰቡ ቀላል አገልግሎት ይሰጣል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2018። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ እንዳሉት አገልግሎቱን ወደ ወረዳዎችና ታዳጊ ከተማዎች ለማስፋፋት ጥረት እየተደረገ ነው። ይህም መንግሥት በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ትጃኒ ናስር አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ በሕብረተሰቡ ላይ የሚደርሰውን እንግልት እንደሚያስቀር ገልጸዋል። በሊሙ ገነት ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል በ8 መስኮቶች 87 የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጣል።
ከ150 ሚሊየን ብር በላይ በወጪ የተገነባው ሕንጻ ውስጥ የተጀመረው አገልግሎት በተጨማሪ በጅማ ዞን ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።