የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2025/26 በጀት ዓመት 80 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል። ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ በመግለጫቸው ባንኩ በተለያዩ ዘርፎች 648 ቢሊየን ብር ብድር መስጠቱን አመልክተዋል።
ባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘቡን 2.4 ትሪሊየን ብር ላይ አድርሷል። ከወጪ ንግድ 2.1 ቢሊየን ዶላር በማግኘት በሁለት ዓመታት ውስጥ አጠቃላይ የውጭ ምንዛሪ 5.6 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።
ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ከስድስት ዓመታት በፊት ባንኩ 90 በመቶውን ብድር ለመንግሥት ተቋማት ያበድር እንደነበር ገልጸዋል። በዚህ ዓመት ግን 588 ቢሊየን ብር ወይም 90 በመቶውን ለግል ዘርፍ ማበደሉን አብራርተዋል።
ባንኩ 546 ቢሊየን ብር ብድር በማሰባሰብ 91 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። ለቀጣዩ ዓመት 832 ቢሊየን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ለማሰባሰብ እና 360 ቢሊየን ብር ገቢ ለማድረስ እቅድ አለው።