የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ ባለፉት 10 ወራት 600 ቢሊየን 233 ሚሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ። ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ይህ የእቅዱን 100.2 በመቶ ይወክላል።
ኮሚሽነሩ የተከታታይ ሪፎርም ሥራዎች ለዚህ ስኬት ዋነኛው ምክንያት መሆናቸውን አመልክተዋል።
የዚህ ዓመት አፈፃፀም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር 256 ቢሊየን ብር ብልጫ አሳይቷል። ኮሚሽኑ በሕገወጥ ተግባራት ሊጠፋ የነበረውን 228.7 ቢሊየን ብር ማዳን ችሏል።
በኮንትሮባንድ እና ንግድ ማጭበርበር ቁጥጥር ስራዎች 1,295 ግለሰቦችን ለሕግ ማቅረብ ተችሏል።