የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከዱባይ ፖሊስ ጋር በመተባበር ሁለት አደገኛ ሕገወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ። ተጠርጣሪዎቹ 105 ዜጎችን በማታለል ከ188 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስበዋል።
ዳውድ ተፈሪ እና ደስታ ተገኝ የተባሉት ተጠርጣሪዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ወጣቶችን በማታለል ወደ ዱባይ ይልኩ ነበር። በተዘጋጀ ቦታ በማገት ሴቶችን በጾታዊ ጥቃትና ማሰቃየት ይፈጽሙ ነበር።
ተጎጂዎች ከአንድ ሰው 320 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር እንዲከፍሉ ተደርገዋል። ወደ ዱባይ ከገቡ በኋላ ተጨማሪ ገንዘብ በመጠየቅ ለሁለት ወር ቪዛ ማለቂያ ሲደርስ ማስፈራሪያ ያደርጉ ነበር።
ፌዴራል ፖሊስ በአገር ውስጥ 1ኛ ብዙአየሁ አውግቸው እና 2ኛ ራህመት አበበ የተባሉ ተባባሪዎቻቸውንም በቁጥጥር ስር አውሏል። ምርመራው በቴክኖሎጂ እና በቀጥታ ቨርቹዋል ምስክርነት እየተካሄደ ነው።