የኦሮሚያ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ በ2018 ዓ.ም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ100 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ማስቀረት መቻሉን አስታውቀዋል።
በኦሮሚያ ክልል በ2018 ዓ.ም በተካሄዱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ከ100 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መቆጠቡ ተገልጿል።
ሳዳት ነሻ በትምህርት፣ በጤና፣ በደም ልገሳ እና አቅመ ደካሞችን በመደገፍ አዎንታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ይህም በህብረትና በአንድነት የሚገኝ ውጤት መሆኑን አመልክተዋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ የ2019 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ተጀምሯል። ይህ ስራ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል።